ፍርድ ቤቱ ሐሰተኛ የቃለ-መሐላ አቤቱታ ያቀረቡ ባለጉዳይን በችሎት መድፈር እንዲቀጡ ወሰነ

360

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሶስተኛ ሰበር ችሎት ሐሰተኛ ቃለ-መሐላ አቤቱታ ያቀረቡ ባለጉዳይን በችሎት መድፈር ጥፋተኛ ናቸው በማለት ሐምሌ 27 ቀን 2014 ዓ.ም በዋለው ችሎት በአንድ ወር ከአስራ አምስት ቀን ቀላል እስራት እንዲቀጡ ወሰነ፡

ፍርድ ቤቱ በእስራት እንዲቀጡ የወሰነባቸው አቶ ኃይለማርያም ወዳጆ በደሀ ደንብ መስቀልኛ የሰበር አቤቱታ ለማቅረብ የዳኝነት ለመክፈል ምንም ሀብት እና ንብረት የሌላቸውና በቀበሌ ቤት የሚኖሩ መሆኑን በቃለ-መሐላ በማረጋገጥ አቤቱታቸውን በሀሰተኛ መንገድ በማቅረባቸው ነው፡፡

ዜና መግለጫ

የፌደራል ፍርድ ቤቶች ከነሐሴ 1-30 ባለው ጊዜ መደበኛ የዳኝነት አገልግሎት መስጠታቸውን ይቀጥላሉ

383

በፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/13 አንቀፅ 38(2) መሰረት የፌደራል ፍርድ ቤቶች ከነሐሴ 1 እስከ መስከረም 30 ባለው ጊዜ ዝግ እንደሚሆኑ ይደነግጋል፡፡ በዚህ ጊዜ ውስጥ ዳኞች ባላቸው የትርፍ ጊዜ አስቸኳይ የሆኑ ጉዳዮችን ብቻ ሊያስተናግዱ እንደሚገባም አዋጁ ያስቀምጣል፡፡ ዳኞች ዓመቱን ሙሉ እጅግ አድካሚ የሆነ የዳኝነት አግልግሎት ሲሰጡ ቆይተዋል፡፡ በዚህም አዎንታዊ የሆኑ ውጤቶች ተገኝተዋል፡፡ ይህን ስራ ይበልጥ ለማስቀጠል፣ ወደ 2015 ዓ.ም የሚያልፉ መዝገቦችን ቁጥር ለመቀነስ፣ የበሰሉ መዝገቦችን እልባት ለመስጠት፣ እስረኛ ያለባቸውን መዝገቦች ቅድሚያ ሰጥቶ ለመስራት እንዲያስችል በዳኞች ፈቃደኝነት ላይ በመመስረት የፌዴራል ፍርድ ቤቶቹ ከነሐሴ 1-30/2014 ዓ.ም ባለው ጊዜ መደበኛውን የዳኝነት አገልግሎት መስጠታቸውን የሚቀጥሉ ይሆናል፡፡

«ትልቁ የመሪዎች መለያ አውቃለሁ ባይነት ሳይሆን ለመማር ዝግጁ መሆን ነው»

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ክብርት ወ/ሮ መአዛ አሸናፊ

271

ክብርት ፕሬዚደንትዋ ይህን የገለጹት የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ም/ፕሬዚደንትና የፌደራል ፍርድ ቤቶች ቃል አቀባይ የሆኑት ክቡር አቶ ተስፋዬ ንዋይ «የአመራር ክህሎት» በሚል ርዕስ ያሳተሙትን መጽሐፍ ሐምሌ 2 ቀን 2014 ዓ.ም በሐያት ሪጀንሲ ሆቴል ለማስመረቅና ለማስገምገም በተዘጋጀ ሥነሥርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር ነው፡፡

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤትም ሆነ የዳኞች አስተዳደር ጉባዔ የሰጠው አንድም የዳኝነት ሹመት የለም

339

የፌዴራል ዳኞች አስተዳደር ጉባዔ በአዋጅ ቁጥር 1233/2013 በተሰጠው ስልጣን መሰረት የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የጉዳዮች ፍሰት አስተዳደር መመሪያን ለመተግበር ያስችለው ዘንድ የተከማቹ መዛግብትን በቅድሚያ ማጥራት አስፈላጊ መሆኑን ገልጾ ጊዜያዊ ዳኞች እንዲመደቡለት ያቀረበውን ጥያቄ አቅርቧል፡፡

ይህንን ተከትሎ ጉባዔው በፌዴራል ዳኝት አስተዳደር አዋጅ  ቁጥር 1233/2013 አንቀጽ 26 (2) ከአንድ ፍርድ ቤት ወደ ሌላ የፍርድ ቤት ደረጃ በጊዜያዊነት ዳኞችን መድቦ የማሰራት ስልጣኑን ተጠቅሞ የጠቅላይ ፍርድ ቤት የዳኝነት ሸክምን ይወጣሉ ያላቸውን አራት የከፍተኛ ፍርድ  ቤት ዳኞች ከሰኔ 2014 ዓ.ም እስከ ህዳር 30 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ብቻ የመዝገብ ክምችት እንዲያጠሩ ውሳኔ አሳልፏል፡፡ 

በሃገራችን የሰብዓዊ መብትን ለመጠበቅም ሆነ ለማስከበር በቂ የህግ ማዕቀፍ ያለ መሆኑ ተገለጸ

468

 “ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች አተገባበር በኢትዮጵያ ፍርድ ቤቶች” በሚል ርዕስ  ለፌዴራል ፍርድ ቤቶች ዳኞች እና የህግ ባለሙያዎች የአንድ ቀን ስልጠና ተሰጥቷል፡፡

የስልጠናው ዋና ዓላማ የህዝብ ጥቅም የሚነኩ ክርክሮች ጽንሰ ሃሳባዊ ማዕቀፎችን፣ በኢትዮጵያ ሃገራዊ የዳኝነት ስልጣን ወሰን የሰብዓዊ መብቶችን የተመለከቱ ክርክሮችን ለመዳኘት የሚያግዙ በስራ ላይ ያሉ የህግ ማዕቀፎች እንዲሁም መሰረታዊ መብቶችንና ነጻነቶችን ለመተግበር የሚረዱ የህግ ማዕቀፎችን በስልጠናው ለተሳተፉ ዳኞችና ህግ ባለሙያዎች ማስገንዘብ እና የጋራ መረዳት መፍጠር ነው፡፡

የፍርድ ቤቱን የአስተዳር ሰራተኞች አገልግሎት አሰጣጥ ውጤታማነት የሚያጎለብቱ ስልጠናዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ

255

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ም/ፕሬዝደንት ክቡር አቶ ሰለሞን አረዳ የፍርድ ቤት የአስተዳር ሰራተኞችን አገልግሎት አሰጣጥ ውጤታማነት የሚያጎለብቱ ስልጠናዎችን የመስጠት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገለጹ፡፡

ክቡር አቶ ሰለሞን አረዳ ይህን የገለጹት ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የአስተዳደር ዘርፍ የጽ/ቤት ሃላፊዎች፣ ዳይሬክተሮችና ቡድን መሪዎች በተዘጋጀ ስልጠና ማጠቃለያ ላይ በሰጡት የስራ መመሪያ ነው፡፡

በአስተዳደር ዘርፍ የፍርድ ቤቱን አገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል የሰራተኞውን የመፈጸም ዓቅም ለማጎልበት የሰራ መሆኑ ተገለጸ

357

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በአስተዳደር ዘርፍ የአገልግሎት አሰጣጥን የሚያቀላጥፍ የአቅም ግንባታ ስልጠና 630 ለሚጠጉ የፍርድ ቤቱ የአስተዳደር ሰራተኞች ከግንቦት 04 ቀን 2014 እስከ ግንቦት 21 ቀን 2014 ዓ/ም ቢሾፍቱ በሚገኘዉ የኢትዮጵያ ስራ አመራር ኢንስቲቲዩት በአራት ዙር ሰጥቷል፡፡

ሰበር ሰሚ ችሎቱ ሕጋዊነቱ ባልተረጋገጠ ሁኔታ በእስር ላይ የሚገኙት ኮሎኔል ገሙቹ አያና ከእስር እንዲለቀቁ ትዕዛዝ ሰጠ፡፡

349

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት 3ተኛ ሰበር ሰሚ ችሎት ዛሬ ግንቦት 16 ቀን 2014 ዓ.ም በዋለው ችሎት  ከቀረበባቸው ክስ በከፍተኛ ፍርድ ቤት በነጻ ከተሰናበቱ በኋላ ህጋዊነቱ ባልተረጋገጠ ሁኔታ የተያዙና ይህ ውሳኔ እስከተሰጠበት ቀን ድረስ በእስር ላይ የሚገኙትን ኮሎኔል ገመቹ አያና ከእስር እንዲለቀቁ ወስኗል፡፡  ለፌዴራል ፖሊስም ተጠርጣሪውን በዛሬዋ ዕለት እንዲለቅ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡

First34568101112Last