የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቦሌ ምድብ ችሎት የአንድ መስኮት አገልግሎት እና የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ለሚ ኩራ ምድብ ችሎት የመስክ ጉብኝት ተካሄደ

435

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቦሌ ምድብ ችሎት እና በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ለሚ ኩራ ምድብ ችሎት በመገኘት ጉብኝት አድርገዋል።

የፍርድ ቤት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ መልካም ስነ ምግባርን በመላበስ የተቋሙን ራዕይ ማሳካት እንደሚገባ ተገለጸ

587

በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት መልካም ስነ-ምግባራዊ ባህርይ የተላበሰ አገልግሎት አሰጣጥን ለማጎልበት ስነልቦና፣ ስነምግባርና አገልግሎት አሰጣጥ በሚል ርዕስ መጋቢት 3 ቀን 2017 ዓ.ም የአንድ ቀን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ከተቋሙ ልዩ ልዩ የስራ ክፍሎች ለተዉጣጡ 115 ሰራተኞች ተሰጥቷል፡፡

የወንጀል ቅጣት አወሳሰን መመሪያ ማሻሻያ ረቂቅ ላይ የግብአት ማሰባሰቢያ የምክክር መድረክ ተካሔደ

452

ላለፉት አስራ አንድ ዓመታት በሥራ ላይ የቆየውን የፍርድ ቤቶች የወንጀል ቅጣት አወሳሰን መመሪያ ለማሻሻል ተዘጋጅቶ በቀረበ ረቂቅ መመሪያ ላይ ግብአት ለማሰባሰብ የተዘጋጀና የፌደራል ፍርድ ቤቶችን ጨምሮ ከሁሉም የአገሪቱ ክፍሎች ጥሪ የተደረገላቸው 160 ያህል ዳኞች፣ ዐቃቢያነ ሕግ፣ ጠበቆች እና ሌሎች የሕግ ባለሙያዎች የተሳተፉበት የምክክር መድረክ የካቲት 29 ቀን 2017 ዓ.ም ተካሔደ፡፡

በከባድና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች ላይ የተዘጋጀ ሥልጠና ለፌዴራል እና ክልል ፍርድ ቤቶች ዳኞች ተሰጠ

468

ለፌደራል ፍርድ ቤቶች እና ከሁሉም ክልል ፍርድ ቤቶች ለተውጣጡ ዳኞች እንዲሁም ለወታደራዊ ፍርድ ቤት ዳኞች በከባድና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች ላይ የተዘጋጀ የአንድ ቀን ስልጠና የካቲት 22 ቀን 2017 ዓ.ም ተካሄደ፡፡

የፌደራል ፍርድ ቤቶችን የለውጥ ሥራ ተፈጻሚ ለማድረግ የፍርድ ቤቶችን የሰው ኃይል አቅም መገንባት ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ተገለጸ

463

በፌደራል ፍርድ ቤቶች የተጀመረውን የለውጥ ሥራ ተፈጻሚ ለማድረግ የፍርድ ቤቶችን የሰው ኃይል አቅም መገንባት ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ መሆኑን የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዝደንት ክብርት ወ/ሮ አበባ እምቢአለ ገለጹ፡፡

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ልዑክ ቡድን በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመገኘት ጉብኝት አደረጉ

456

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር፣ሚኒስትር ዴኤታዎች እንዲሁም ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችን ያካተተ የልዑክ ቡድን በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በቀን 18/06/2017 ዓ.ም በመገኘት ጉብኝት አድርገዋል፡፡

የህዝባዊት ቻይና ሪፐብሊክ ፍትህ ሚኒስትር በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመገኘት የስራ ጉብኝት አደረጉ

662

የህዝባዊት ቻይና ሪፐብሊክ ፍትህ ሚኒስትር ሚስ ሂ ሮንግ እንዲሁም በኢትዮጵያ የቻይና ሪፐብሊክ አምባሳደር የሆኑት ሚስተር ቺን ሃይ ከልዑክ ቡድኖቻቸው ጋር በመሆን በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በቀን 6/6/2017 ዓ.ም በመገኘት የጋራ ግንኙነታቸውን በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ላይ ከፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረትና ሌሎች የስራ ሃላፊዎች ጋር በመሆን የስራ ጉብኝትና ውይይት አድርገዋል፡፡

"ስነ ምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልእኮ ስኬት" በሚል መሪ ቃል ለፌደራል ፍርድ ቤቶች መካከለኛ አመራሮች ስልጠና ተሰጠ

508

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከፌደራል ስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ጋር በመተባበር ለፌደራል ፍርድ ቤቶች መካከለኛ አመራሮች "ስነ ምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልእኮ ስኬት" በሚል መሪ ቃል ከፌደራል ፍርድ ቤቶች፣ ከፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ፅ/ቤት እንዲሁም ከፌደራል ፍትህና ህግ ኢንስቲትዩት የተውጣጡ የስራ ኃላፊዎች፣ ቡድን መሪዎችና ሬጅስትራሮች የተሳተፉበት የሁለት ቀናት ስልጠና የካቲት 5 እና 6 2017 ዓ.ም ተሰጥቷል፡፡

First34568101112Last