በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በመምከር ሲካሄድ የቆየው ሀገር አቀፍ የህግ ተርጓሚዎች መድረክ የጋራ አቋም በመያዝ ተጠናቋል።

735

በመድረኩም ከተመረጡ አጀንዳዎች ጋር በተገናኘ ሙያዊ ማብራሪያዎች ቀርበው ሰፊ ውይይት ተደርጎባቸዋል።

በመጨረሻም ለመጪው 1 ዓመት የግንኙነት መድረኩ ምክትል ሰብሳቢ ምርጫ ተደርጎ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዝደንት ክቡር አቶ ኤርሴኖ አቡሬ ተመርጠዋል።

ሀገር አቀፍ የህግ ተርጓሚዎች መድረክ እየተካሄደ ይገኛል

819

የፌደራል እና የክልል ፍርድ ቤቶች ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንቶችን ያካተተ ሀገር አቀፍ የህግ ተርጓሚዎች መድረክ በቀን 27/07/2017 ዓ.ም በቢሾፍቱ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል፡፡

በኢትዮጵያ የፈረንሳይ ኤምባሲ አምባሳደር ክቡር ሚ/ር አሌክስ ላሜክ በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመገኘት ጉብኝት አደረጉ

791

በኢትዮጵያ የፈረንሳይ ኤምባሲ አምባሳደር ክቡር ሚ/ር አሌክስ ላሜክ -በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመገኘት በቀን 18/07/2017 ዓ.ም ጉብኝት አድርገዋል።

የፍርድ ቤት መር አስማሚነት ላይ የሁለት ቀናት ስልጠና ተሰጠ

795

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከፌደራል የፍትሕና ሕግ ኢንስቲትዩት እና ከኢትዮጵያ የማስማማትና ግልግል ዳኝነት ማዕከል (EMAC) ጋር በመተባበር የሁለት ቀናት ስልጠና ለፌደራል ከፍተኛ እና መጀመሪያ ፍርድ ቤት ረዳት ዳኞች ተሰጥቷል፡፡

ስዊድን አገር ለተደረገው የስራ ጉብኝትና ልምምድ ልውውጥ ስኬት ላበረከቱ አካላት የምስጋና መርኀ ግብር ተካሄደ፡፡

837

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከአውሮፓ ህብረት በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ እያከናወነ ከሚገኘው የወንጀል ፍትህ አስተዳደር መሻሻያ ተግባራት መካከል በወንጀል ፍትህ አስተዳደር የተሻለ ተሞክሮ ካላቸው አውሮፓ አገራት ፍርድ ቤቶች ልምድ መቅሰም ይገኝበታል። ይህንኑ ተከትሎ በቅርቡ 23 የፌደራል ፍርድ ቤቶች ዳኞች ወደ ስዊድን አገር በመጓዝ ከአገሪቱ ፍ/ቤቶች ልምምድ መቅሰማቸው ይታወቃል፡:

የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቦሌ ምድብ ችሎት የአንድ መስኮት አገልግሎት እና የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ለሚ ኩራ ምድብ ችሎት የመስክ ጉብኝት ተካሄደ

731

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቦሌ ምድብ ችሎት እና በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ለሚ ኩራ ምድብ ችሎት በመገኘት ጉብኝት አድርገዋል።

የፍርድ ቤት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ መልካም ስነ ምግባርን በመላበስ የተቋሙን ራዕይ ማሳካት እንደሚገባ ተገለጸ

1011

በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት መልካም ስነ-ምግባራዊ ባህርይ የተላበሰ አገልግሎት አሰጣጥን ለማጎልበት ስነልቦና፣ ስነምግባርና አገልግሎት አሰጣጥ በሚል ርዕስ መጋቢት 3 ቀን 2017 ዓ.ም የአንድ ቀን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ከተቋሙ ልዩ ልዩ የስራ ክፍሎች ለተዉጣጡ 115 ሰራተኞች ተሰጥቷል፡፡

የወንጀል ቅጣት አወሳሰን መመሪያ ማሻሻያ ረቂቅ ላይ የግብአት ማሰባሰቢያ የምክክር መድረክ ተካሔደ

768

ላለፉት አስራ አንድ ዓመታት በሥራ ላይ የቆየውን የፍርድ ቤቶች የወንጀል ቅጣት አወሳሰን መመሪያ ለማሻሻል ተዘጋጅቶ በቀረበ ረቂቅ መመሪያ ላይ ግብአት ለማሰባሰብ የተዘጋጀና የፌደራል ፍርድ ቤቶችን ጨምሮ ከሁሉም የአገሪቱ ክፍሎች ጥሪ የተደረገላቸው 160 ያህል ዳኞች፣ ዐቃቢያነ ሕግ፣ ጠበቆች እና ሌሎች የሕግ ባለሙያዎች የተሳተፉበት የምክክር መድረክ የካቲት 29 ቀን 2017 ዓ.ም ተካሔደ፡፡

First45679111213Last