የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክብርት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሹመታቸውን ያጸደቀላቸው የኢትዮጵያ አገራዊ የምክክር ኮሚሽን አመራሮች የቃለመሀላ ሥነ-ሥርዓት ዛሬ የካቲት 14 ቀን 2014 ዓ.ም አስፈጽመዋል፡፡
ክብርት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ የአገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ስራ ውጤታማ የሚሆነው ከባለድርሻ አካላት እና ከሕብረተሰቡ አስፈላጊው ትብብርና ድጋፍ ሲሰጠው መሆኑን በቲውተር ገጻቸው ገልጸዋል፡፡
ክብርት ፕሬዝደንቷ ከምክክር ኮሚሽኑ ብዙ ይጠበቃልም ብለዋል::