ዓርብ ፣ ግንቦት 30 ቀን 2025 / Categories: CASSATION, Cassation ቻይና ሬል ወይስ ሰቨንዝ ግሩፕ ኦሞ ወንዝ ታርጫ መንገድ ስራ ድርጅት እና አቶ ደረሰ ደሳለኝ -የሰ/ መ/ ቁ 254490 ፍርድ ቤት በሰጠው ውሳኔ ቅር በመሰኘት የአሁን አመልካች ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 18418 ይግባኝ ያቀረቡ ሲሆን ፍርድ ቤቱም በቀን 05/12/2015 አ.ም ይግባኙ አያስቀርብም በማለት ሰርዞታል፡፡ የአሁን አመልካች በነዚህ ውሳኔዎች ላይ ቅር በመሰኘት ለዚህ ሰበር ሰሚ ችሎት በቀን 23/02/2016 አ.ም የተፃፈ የሰበር አቤቱታ አቅርበዋል፡፡ ይዘቱም ተጠሪ በክሳቸው እንዲወሰንላቸው የጠየቁት የዳኝነት መጠን ብር 800,800 (ስምንት መቶ ሺህ ስምንት መቶ ብር) ካሣ ሆኖ እያለ ህጉን ባልተከተለ መንገድ፣ ገለልተኛ ባልሆኑ ሰዎችና ቦታው ላይ እንዳልገኝ ተደርጎ ከቅን ልቦና ውጪ ከሳሽ ከጠየቀው ዳኝነት በላይ የተሰራዉ የባለሞያ ማጣሪያ አመልካችን እጅግ የሚጎዳ በመሆኑና የሞያው ባለቤት በሆነው በከርሰ ምድር ባለሞያ እንዲጣራ ተደርጎ የተጎዳ ንብረት ካለ በግራ ቀኙ ገማች ኮሚቴ አባላት ተመርጠው እንዲገምቱ ተደርጎ ውሳኔ እንዲሰጠኝ በስር ፍርድ ቤት ጠይቄ እያለ ይህ ሳይደረግ የተሰጠው ውሳኔ መሰረታዊ የህግ ስህተት ያለበት በመሆኑ ተሸሮ ከወጪና ኪሳራ ጋር እንዲወሰንልኝ በማለት የሰበር አቤቱታቸውን አቅርበዋል፡፡ መልካም ንባብ… Print 4131 Documents to download 254490(.pdf, 838.66 KB) - 522 download(s)