አቶ አየለ ሽፈራው እና ጎባ ወረዳ ፍ/ቤት ጎባ ወረዳ ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት የሰ/መ/ቁ. 255190
ጉዳዩ የመንግሥት ሠራተኛን ከሥራና ከደመወዝ ማገድ ሕጋዊነትን የሚመለከት ነው፡፡ የሰበር አቤቱታው የቀረበው የደ/ም/ኢት/ክ/መ/ጠ/ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የሠጠው ውሳኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ተፈጽሞበታል በሚል ነው፡፡ የክርክሩን አመጣጥ ከስር ፍርድ ቤት የመዝገብ ግልባጭ እንደተረዳነው በሥር ፍርድ ቤት አመልካች ይግባኝ ባይ ሲሆን ተጠሪዎች መልስ ሰጪዎች ነበሩ፡፡ ተጠሪ በ22/03/2015 ዓ/ም ለአስተዳደር ፍ/ቤት ጽፈው ባቀረቡት የይግባኝ ቅሬታ ተጠሪዎች የትምህርት ማስረጃዬ ሀሰተኛ ስለመሆኑ ባላረጋገጡበት ዲፕሎማ ሰርተፍኬትህ ሀሰተኛ ነው በማለት ከስራ እና ደመወዝ ያለአግባብ ያገዱኝ ስለሆነ ወር ደመወዜ ከተቋረጠበት ከጥቅምት 1 ቀን 2015ዓ.ም ጀምሮ ተከፍሎኝ ወደ ሥራ እንድመለስ እንዲወሰንልኝ በማለት ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡
1663
Documents to download
-
255190(.pdf, 863.92 KB) - 206 download(s)