እነ ፋጡማ ኢብራሂም (5) ሰዎች እና መፍቱሃሙሳ የሠ/መ/ቁጥር 257851
የሰበር ቅሬታው ይዘት በአጭሩ፡- የምሰራቅ ሐረርጌ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት መስከረም 4 ቀን 2016 ዓ.ም ክርክሩ ሊቀጥል አይገባም በሚል ቀርቦለት የነበረውን አቤቱታ ውደቅ ካደረገ በኋላ የፍትሐ ብሔር ሥነ ሥርዓት ሕጉን ቁጥር 208 ድንጋጌን መሠረት አድርጎ ጥቅምት 12 ቀን 2016 ዓ.ም የቀረበውን ተመሳሳይ አቤቱታ በድጋሚ አይቶ አስቀድሞ የሰጠውን ትዕዛዝ መሻሩ፤ የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚው ችሎት የፌዴራሽን ምክር ቤት የህግ ትርጉም እስኪሰጥ ድረስ ክርክሮች ታግደው እንዲቆዩ መመሪያ ያስተላለፈው በአዲስ አበባ ከተማ እና በኦሮሚያ ክልል ነዋሪ በሆኑ ተከራካሪዎች መካከል የሚደረገውን ክርክር የሚመለከት እንጅ በኦሮሚያ እና የሀረሪ ክልል ነዋሪዎችን የማይመለከት ሆኖ ሳለ የሰበር ሰሚ ችሎቱ የሰጠው ትዕዛዝ ተጠቅሶ ክርክሩ መቋረጡ፤የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚው ችሎት የክልል ያልሆነ(በፌደራል ጉዳይ) በመመሪያ የማስቆም ሥልጣን የለሌለው መሆኑ እየታወቀ መመሪያውን መሠረት አድርጎ መዝገቡ መዘጋቱ፤ ይግባኝ ሰሚው የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤትም ይህንኑ ትዕዛዝ ማጽናቱ በሕገ-መንግስቱ የተከበረላቸውን መብት የሚጥስ ስለሆነ የሥር ፍርድ ቤቶች የሰጡት ትእዛዝ እና ውሳኔ ተሽሮ መዝገቡ ከቆመበት ተንቀሳቅሶ ውሳኔ እንዲሰጥ ይወሰንልን የሚል ነው፡፡መልካም ንባብ…
2067
Documents to download
-
257851(.pdf, 869.55 KB) - 256 download(s)