ወ/ሮ ሰላማዊት ያደሳ እነ አቶ ፀሀዬ ጌታቸው(2ሰዎች) የሠ/መ/ቁጥር 256923
ጉዳዩ አመልካች ከ1ኛ ተጠሪ ጋር እንደባልና ሚስት አብረዉ በኖሩበት ጊዜ ያፈራነዉ ንብረት ነዉ ያሏቸዉን ንብረቶች ለመካፈል ያቀረቡት ክስ አስቀድሞ ዉሳኔ ባገኘ ጉዳይ ለሁለተኛ ጊዜ የቀረበ ክስ ነዉ በሚል ዉድቅ በመደረገ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ተፈጽሞበታል በሚል በቀረበ የሰበር አቤቱታ መነሻ የተደረገዉን ክርክር የሚመለከት ነዉ፡፡ ክርክሩ በተጀመረበት በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አመልካች በ1ኛ ተጠሪ ላይ በመሰረቱት ክስ የአሁን 2ኛ ተጠሪ ጣልቃ በመግባት የተከራከሩ ሲሆን የክሱ ይዘት በአጭሩ - ከ1ኛ ተጠሪ ጋር ከቀን 15/04/1999 ዓ.ም ጀምሮ እንደባልና ሚስት አብረን ስንኖር ያፈራነው በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 ክልል ውስጥ የሚገኝ የቤት ቁጥር 121 የይዞታ መለያ ቁጥር AA000070806106 የሆነና በተጠሪ ስም ተመዝግቦ የሚገኝ ስፋቱ 403 ካሬ ሜትር የሆነ 8 የሚከራዩ ሰርቪስ ቤቶች እና 4 ክፍል ያለው ዋና ቤት እና ቦታ የጋራ ሀብት ስለሆነ ተጠሪ ድርሻዬን እንዲያካፍለኝ በማለት ሌሎች ንብረቶችንም እንደዚሁ በመጥቀስ ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡ መልካም ንባብ…
3190
Documents to download
-
256923(.pdf, 1.2 MB) - 441 download(s)