ወ/ሮ ኢየሩሳሌም ኃይሉ እና እነ ወ/ሮ እታገኘው ኃይሉ(4ሰዎች) የሰ/መ/ቁጥር 253718
ጉዳዩ የውርስ ማጣራትን ተከትሎ የውርስ ሀብት ስለመሆኑ በተለየ ንብረት ላይ መብት ያላቸው ወራሾች ሊያገኙ ይችሉ የነበረውን ገቢ ቤቱን ከያዘው ሰው ለመጠየቅ ያላቸውን መብት የሚመለከት ነው፡፡ክርክሩ የተጀመረው በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ሲሆን 1ኛ፣2ኛ እና 3ኛ ተጠሪዎች ከሳሾች፣4ኛተጠሪ ጣልቃገብ አንደዚሁም አመልካች ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡በተጠሪዎች የቀረበው ክስ በአጭሩ ሟቾች አቶ ሀይሉ ደነቀው እና ወ/ሮ ልንገርሽ ይሁኔ በ422 ካ.ሜ ላይ ያረፈና የቤት ቁጥር 191 የሆነ ዋና ቤትና ሰርቪስ ቤቶች የነበሯቸው ሲሆን በመ/ቁ 82464 በፌ/መ/ደ/ፍ/ቤት መናገሻ ምድብ ችሎት በነበረን የውርስ ሀብት ይጣራልን ክርክር ላይ የሟች አቶ ኃይሉ ደነቀው የውርስ ሀብት ተጣርቶ ውሳኔ ተሰጥቷል፡፡አመልካች በኑዛዜ የተላለፈላቸው 02 ክፍል ቤት ብቻ ሲሆን ክፍሎቹን እያከራዩ የሚጠቀሙበት ሆኖ በውርስ የሚደርሰንን ዋና ቤትና ሰርቪስ ቤቶችን ከህግ አግባብ ውጪ በመያዝ በዋናው ቤት እየኖሩበት አከራይተን እንዳንጠቀም በማድረግ ሰርቪስ ቤቶቹን ከተከራዩት ሰዎች ላይ የኪራዩን ገንዘብ በመሰብሰብ ለራሳቸው ጥቅም በማዋል ልናገኝ የሚገባውን ጥቅም አሳጥተውናል፡፡በመሆኑም በውሳኔው መሰረት የሚኖሩበትን ዋናውን ባለ ሶስት ክፍሉን ቤት እና የምያከራዩትን 03 ክፍል ሰርቪስ ቤቶች ከነቦታው ለቀው እንዲያስረክቡን በተደጋጋሚ ከመጠየቅ ባሻገር ጥቅምት 29 ቀን 2014 ዓ.ም ደግሞ የጹሑፍ ማስጠንቀቂያ የሰጠናቸው ቢሆንም አመልካች ቤቶቹን ለማስረከብ እንደዚሁም የቤቶቹ ኪራይ ገንዘብ ለመክፈል ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ሟች ከሞቱበት ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ ዋናው ቤት ቢከራይ በወር ብር 8000 (ስምንት ሺህ) ክስ እስካቀረብንበት ጊዜ ድረሰ ያለውን የ28 ወር ብር 224,000.00 (ሁለት መቶ ሀያ አራት ሺህ) እንዲከፍሉን፣የሚከራዩ 3 (ሶስት) ክፍል ሰርቪስ ቤቶች ሟች ከሞቱበት ጊዜ ጀምሮ እስከ ሚያዚያ ወር ብር 1500 (አንድ ሺ አምስት መቶ) ይከራይ የነበረው አመልካች ብር 300 (ሶስት መቶ) በመጨመር ብር 1800 (አንድ ሺ ስምንት መቶ)፣ ሌላው 1 (አንድ) ክፍል ቤት 500 (አምስት መቶ) ይከራይ ነበረው ብር 700 (ሰባት መቶ) እና ቀሪውን 01 ክፍል ቤት በብር 1000 (አንድ ሺህ) ልዩነቱ የ4 (አራት) ወር ብር 4000 (አራት ሺ) ሟች ከሞቱበት ጊዜ ጀምሮ እስከ መጋቢት ወር መጨረሻ ክስ እስካቀረብንበት ጊዜ ድረስ ያለው ሲሰላ ሁለት ዓመት 24 (ሀያ አራት) ወር በመሆኑ ብር 70,000.00 (ሰባ ሺህ) በድምሩ ብር 74,000 (ሰባ አራት ሺህ) ልናገኝ የሚገባውን ጥቅም ያሳጡን ስለሆነ ዋናውን ቤት እና የሰርቪስ ቤቶቹን የኪራይ ገንዘብ ተከፍሎ እስከሚጠናቀቅበት ድረስ ከነወለዱ ታስቦ እንድከፍሉን እንዲወሰንልን የሚል ነው፡፡መልካም ንባብ…..
3167
Documents to download
-
253718(.pdf, 1.07 MB) - 411 download(s)