ዊነርስ ቻፕል ኢንተርናሽናል እና እነ አቶ አለማየሁ ወዳጅ መንግስቱ /2 ሰዎች/ የሰበርመ/ቁ/257342
ከመዝገቡ መረዳት እንደሚቻለው ተጠሪዎች ባቀረቡት ክስ ከአመልካቸ ጋር የነበራቸዉ የሰራ ግንኝነት የተቋረጠ በመሆኑ የተለያዩ ክፍያዎች እንዲከፈላቸዉ የጠየቁ ሲሆን አመልካች በቀረበዉ ክስ ላይ መልስ እንዲያቀርብ ትዕዛዝ ተልኮ ነገር ግን ተጠሪዎች አመልካች መጥርያ ለመቀበል ፍቃደኛ አለመሆኑን በቃለ መኃላ አረጋግጠዉ በመቅረባቸዉ ፍርድ ቤቱ የአመልካች በፁሁፍ መልስ የማቅረብ መብቱን አልፎ ክስ ለመስማት በተቀጠረበት ቀንም አመልካች ባለመቅረቡ ጉዳዩን አመልካች በሌለበት አከራክሮ ዉሳኔ ሰጥቷል፡፡ በሰጠው ውሳኔ የስራ ውሉ የተቋረጠው በተጠሪዎች በራሳቸው ፈቃድ መሆኑን፤ እንዲሁም ክፍያን አስመልክቶ የሁለት አመት የትርፍ ሰዓት ክፍያን ጨምሮ የተለያዩ ክፍያዎች ለተጠሪዎች እንዲከፈል ወስኗል፡፡ መልካም ንባብ ….
1989
Documents to download
-
257342(.pdf, 840.52 KB) - 276 download(s)