Login
Federal Supreme Court
Search
  • ዋና ገፅ
  • ስለ ፍርድ ቤቱ
    • የዳኝነት ታሪክና ስርዐት
    • ራዕይ፣ ተልዕኮና የተሰጠ ኃላፊነት
    • ፕሬዝደንት
      • በስራ ላይ ያሉ ፕሬዝደንት
    • ም/ፕሬዝደንት
      • በስራ ላይ ያሉ ም/ፕሬዝደንት
      • የቀድሞ ም/ፕሬዚደንቶች
    • ዳኞች
      • በስራ ላይ ያሉ ዳኞች
      • የቀድሞ ዳኞች
    • አስተዳደር እና ዳይሬክቶሬቶች
  • የፍርድ ቤቱ አገልግሎቶች
    • የሬጂስትራር አገልግሎት
      • የተለያዩ የፍ/ቤት ፎርሞች
    • የፍርድ ቤቱ ዕለታዊ መርሐ-ግብር
    • የጉዳዮች መከታትያ
    • የፍርድ ቤት ሰነዶችን ለመጠየቅ
      • ውሳኔ ያገኙ ጉዳዮችን ለመጠየቅ
    • የህግ ድጋፍ
      • የተከላካይ ጠበቆች አገልግሎት
    • የፍርድ ቤት መር አስማሚነት
    • የትርጉም አገልግሎት
  • ኢ-ፋይሊንግ
    • Quick Start Guide
      • መመዝገብ
      • ኢ-መዝገብ መክፈት
    • የአጠቀቃቀም መግለጫ
    • ደንቦችና መመሪያዎች
    • ቅጾች
    • ማስተማሪያዎች እና ማሳያዎች
  • ወደ ፍርድ ቤት ሲሄዱ
    • በፍርድ ቤት ሲገኙ
      • ምን ማየት እና ማድረግ እችላለሁ?
    • የችሎት ውስጥ ሥነሥርዓት
      • ችሎት ስርዓት ደንቦች
    • መረጃ ለወንጀል ተጠርጣሪዎች/ተከሳሾች
    • መረጃ ለፍትሐብሔር ተከራካሪዎች
    • በፍርድ ቤት ራስን ስለመወከል
    • መረጃ- ምስክር ሆነው ለሚቀርቡ
    • መረጃ ለሕግ ባለሙያዎች
    • በተደጋጋሚ የሚቀርቡ ጥያቄዎች
  • ዲጂታል የሕግ ቤተ መጽሐፍት
    • ዓመታዊ ሪፖርቶች
    • የፍርድ ቤቱ አሁናዊ ሁኔታ
    • የዳኞች ወርሐዊ ጉባዔ
    • በፌደራል መንግሥት የወጡ ሕጎች
    • የተለያዩ ሰነዶች
    • የህትመት ውጤቶች
      • የህግ መጽሄት
      • የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔ ቅፅ
      • ጋዜጣ
    • ውሳኔዎች
      • ሰበር ውሳኔዎች
      • የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ይግባኝ ውሳኔዎች
  • ዜናዎች
    • መግለጫዎች
    • ምስሎችና ሌሎች
      • ፎቶዎች
      • ተንቀሳቃሽ ምስሎች
    • ለመገናኛ ብዙሃን
      • ዜና መግለጫዎች
      • የፍርድ ቤት ውሎ አዘጋገብ ጥቆማዎች
      • ንግግሮች
  • መገናኛ
    • የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት
    • የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት
    • የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት
    • አስተያየት መስጫ
  • የጨረታ-ማስታወቂያ
  • የፍርድ አፈጻጸም ዳይሬክቶሬት
    • ስለ ፍርድ አፈጻጸም ዳይሬክቶሬት
    • የሐራጅ ማስታወቂያ
  • የህጻናት ፍትህ ፕሮጀክት-
    • መጀመሪያ
    • እኛን ለማግኘት
    • አጋር ድርጅቶች
    • አገልግሎቶች
    • አርቲክሎች
    • ዜናዎች
    • ጋለሪ
  • ክፍት የስራ ማስታወቂያ
ዓርብ ፣ ግንቦት 30 ቀን 2025
/ Categories: CASSATION, Cassation

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ገቢዎች ቢሮ ዓቃቤ ሀግ እና ወ/ሮ መዓዛ በልስቲየሠ/መ/ቁጥር 248735

ጉዳዩ ያለደረሰኝ ግብይት የማከናወን የወንጀል ክስን የሚመለከት ሆኖ ክሱ የቀረበው በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ደጀን ወረዳ ፍርድ ቤት ሲሆን በአመልካች እና በሰበር ክርክሩ የሌሉት ሁለት ግለሰቦች ላይ ቀርቦ የነበረው ክስ፡- የክልሉን የታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 241/2008 አንቀጽ 131/1 እና 119/1 ሥር የተመለከተውን በመተላለፍ በግብር ከፋይ መለያ ቁጥር 0052005902 ፤ በንግድ ምዝገባ ቁጥር AM/EG/DEJEN/1/0001230/2010 በተጠሪ ስም የተመዘገበ በደጀን ከተማ 01 ቀበሌ በሚገኘው ሆቴልና ሉካንዳ ቤት የንግድ ሥራ በደረጃ “ለ” ግብር ከፋይነት ተሰማርተው የድርጅቱ ሥራ አስኪያጅና ባለቤት ሁነው እየሰሩ እያለ ሚያዝያ 6 ቀን 2014 ዓ.ም ከቀኑ በግምት 5:50 ሰዓት ላይ ደርብ አበጀና አፀደ ከተማው የተባሉ ደንበኞች አንድ በየአይነቱ ምግብ እና አንድ ሊትር የታሸገ ውሃ ተጠቅመው ደርብ አበጀ የተባለው ለተጠቀሙበት ክፍያ ብር 200.00(ሁለት መቶ) ለአስተናጋጅ ሲሰጥ የብር 135.00 (አንድ መቶ ሰላሳ አምስት) ሽያጭ ያለደረሰኝ ፈጽመዋል የሚል ነው፡፡

ተጠሪም የእምነት ክህደት ቃላቸውን ተጠይቀው ከአዲስ አበባ የሂክምና ቀጠሮ ስለነበራቸው ወንጀሉ ተፈጽሟል በተባለበት ቦታ ያልነበሩ መሆኑን፤ያለደረሰኝ ግብይት ይፈፀም አይፈፀም እንደማያውቁ፤ የድርጅቱን ሥራ በአግባቡ እንዲሰሩ ለሥር ለሥር 2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾች እንዳሳወቁ ገልጸው ጥፋተኛ አይደለሁም በማለት ተከራክረዋል፡፡ ፍርድ ቤቱም የዐቃቤ-ሕግ ምስክሮች የሰጡትን የምስክርነት ቃል ሰምቶ ወንጀሉ ተፈጽሟ በተባለት ቀንና ሰዓት ተጠሪ በድርጅቱ ውስጥ አለመኖራቸው በቃቤ-ሕግ ምስክሮች መነገሩን ጠቅሶ አመልካች የሥር 2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾች በተመደቡበት የስራ ኃላፊነት ብቁ ሠራተኞች መሆናቸውን በማመን ወደ ህክምና የሄዱ መሆኑ ተረጋግጧል በሚል በወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕጉ ቁጥር 141 መሠረት በነፃ ያሰናበተ ሲሆን፤አመልካች ተጠሪ ከክሱ በብይን በነፃ መሰናበታቸውን በመቃወም ያቀረበው የይግባኝ አቤቱታ በወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 195 መሠረት መሰረዙን ተከትሎ አመልካች ያቀረበውን የሰበር አቤቱታ የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰበር አጣሪ ችሎት ጉዳዩ የፌደራል በመሆኑ ለክልል ሰበር ሰሚ ችሎት ሊቀርብ አይገባም በሚል ሳይቀበለው ቀርቷል፡፡      

የሰበር ቅሬታ የቀረበው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰበር አጣሪ ችሎት ጉዳዩ የፌዴራል ነው በሚል የሰበር አመልካች ያቀረቡትን የሰበር አቤቱታ ባለመቀበል የሰጠውን ፍርድ በመቃወም ሆኖ የሰበር ቅሬታው በአጭሩ፡- ተጠሪ በደጀን ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት በሆቴልና ሉካንዳ ቤት ንግድ ዘርፍ በደረጃ “ለ” በክልል ግብር ከፋይነት ተመዝግበው ሲሰሩ በክልሉ የገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 240/2008 አንቀፅ 79/2 እንዲሁም በታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 241/2008 አንቀፅ 19/3 የተመለከተውን ደረሰኝ የመስጠት ግዴታቸውን ባለመወጣታቸው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 241/2008 አንቀፅ 131/1 እና 119/1 የተመለከተውን በመተላለፍ በፈፀሙት ወንጀል በደጀን ወረዳ ፍርድ ቤት ክስ ቀርቦባቸው ክርክር ተደርጎ የወረዳው ፍርድ ቤት በመጀመሪያ ደረጃ ሥልጣኑ ክርክሩን አይቶ የሰጠውን ውሳኔ የምስራቅ ጎጃም ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤትም በይግባኝ ሰሚነቱ የተመለከተውን የመጨረሻ ውሳኔ ያገኘን የክልል ጉዳይ ተጠሪ በክልሉ የደረጃ “ለ” ግብር ከፋይ እንጅ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ ባልሆኑበት በክልል ግብር ከፋይነታቸው ለፈፀሙት የወንጀል ጥፋት ተጠያቂ የሚሆኑት በክልል የታክስ አስተዳደር አዋጅ መሆኑ እየታወቀ የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰበር አጣሪው ችሎት ጉዳዩን የማየት የሥረ-ነገር ሥልጣን የለኝም በማለት አመልካች ያቀረበውን የሰበር አቤቱታ አለመቀበሉ የአማራ ብሔራዊ ክልል ፍርድ ቤቶችን ለማቋቋም የወጣውን አዋጅ ቁጥር 223/2007 አንቀፅ 17/1 ፤ እንዲሁም የክልሉን ፍርድ ቤቶች ለማቋቋም ተሻሽሎ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 281/2014 አንቀፅ 24 ድንጋጌዎችን የሚቃረን መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈፀመበት ነው በማለት በሰበር ሰሚ ችሎቱ እንዲታረምላቸው ጠይቃዋል፡፡መልካም ንባብ…

Print
3393

Documents to download

  • 248735(.pdf, 1.07 MB) - 388 download(s)

Categories

  • 2011 Expand/Collapse
  • 2012 Expand/Collapse
  • 2013 Expand/Collapse
    መገናኛ
  • ስልክ : +251-11-1-55-34-00 /
  •          +251-11-1-11-04-32
  • ፋክስ : +251 111-550278 /
  •          +251 111-565583
  • ኢሜል : fscpublicrelation@gmail.com
  • አድራሻ ፡ 6 ኪሎ አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
ፈጣን አገናኝ
  • ስለፍርድ ቤቱ 
  • ኢ-ፋይሊንግ
  • የቀን መቁጠሪያ
  • ዜና መግለጫዎች
  • የጉዳዮች መከታተያ
  • በተደጋጋሚ የሚቀርቡ ጥያቄዎች
    ያግኙን
  • Privacy Policy
  • |
  • Site Map
Copyright 2026 by Federal Supreme Court
Powered By Bsquare IT Solutions