Login
Federal Supreme Court
Search
  • ዋና ገፅ
  • ስለ ፍርድ ቤቱ
    • የዳኝነት ታሪክና ስርዐት
    • ራዕይ፣ ተልዕኮና የተሰጠ ኃላፊነት
    • ፕሬዝደንት
      • በስራ ላይ ያሉ ፕሬዝደንት
    • ም/ፕሬዝደንት
      • በስራ ላይ ያሉ ም/ፕሬዝደንት
      • የቀድሞ ም/ፕሬዚደንቶች
    • ዳኞች
      • በስራ ላይ ያሉ ዳኞች
      • የቀድሞ ዳኞች
    • አስተዳደር እና ዳይሬክቶሬቶች
  • የፍርድ ቤቱ አገልግሎቶች
    • የሬጂስትራር አገልግሎት
      • የተለያዩ የፍ/ቤት ፎርሞች
    • የፍርድ ቤቱ ዕለታዊ መርሐ-ግብር
    • የጉዳዮች መከታትያ
    • የፍርድ ቤት ሰነዶችን ለመጠየቅ
      • ውሳኔ ያገኙ ጉዳዮችን ለመጠየቅ
    • የህግ ድጋፍ
      • የተከላካይ ጠበቆች አገልግሎት
    • የፍርድ ቤት መር አስማሚነት
    • የትርጉም አገልግሎት
  • ኢ-ፋይሊንግ
    • Quick Start Guide
      • መመዝገብ
      • ኢ-መዝገብ መክፈት
    • የአጠቀቃቀም መግለጫ
    • ደንቦችና መመሪያዎች
    • ቅጾች
    • ማስተማሪያዎች እና ማሳያዎች
  • ወደ ፍርድ ቤት ሲሄዱ
    • በፍርድ ቤት ሲገኙ
      • ምን ማየት እና ማድረግ እችላለሁ?
    • የችሎት ውስጥ ሥነሥርዓት
      • ችሎት ስርዓት ደንቦች
    • መረጃ ለወንጀል ተጠርጣሪዎች/ተከሳሾች
    • መረጃ ለፍትሐብሔር ተከራካሪዎች
    • በፍርድ ቤት ራስን ስለመወከል
    • መረጃ- ምስክር ሆነው ለሚቀርቡ
    • መረጃ ለሕግ ባለሙያዎች
    • በተደጋጋሚ የሚቀርቡ ጥያቄዎች
  • ዲጂታል የሕግ ቤተ መጽሐፍት
    • ዓመታዊ ሪፖርቶች
    • የፍርድ ቤቱ አሁናዊ ሁኔታ
    • የዳኞች ወርሐዊ ጉባዔ
    • በፌደራል መንግሥት የወጡ ሕጎች
    • የተለያዩ ሰነዶች
    • የህትመት ውጤቶች
      • የህግ መጽሄት
      • የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔ ቅፅ
      • ጋዜጣ
    • ውሳኔዎች
      • ሰበር ውሳኔዎች
      • የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ይግባኝ ውሳኔዎች
  • ዜናዎች
    • መግለጫዎች
    • ምስሎችና ሌሎች
      • ፎቶዎች
      • ተንቀሳቃሽ ምስሎች
    • ለመገናኛ ብዙሃን
      • ዜና መግለጫዎች
      • የፍርድ ቤት ውሎ አዘጋገብ ጥቆማዎች
      • ንግግሮች
  • መገናኛ
    • የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት
    • የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት
    • የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት
    • አስተያየት መስጫ
  • የጨረታ-ማስታወቂያ
  • የፍርድ አፈጻጸም ዳይሬክቶሬት
    • ስለ ፍርድ አፈጻጸም ዳይሬክቶሬት
    • የሐራጅ ማስታወቂያ
  • የህጻናት ፍትህ ፕሮጀክት-
    • መጀመሪያ
    • እኛን ለማግኘት
    • አጋር ድርጅቶች
    • አገልግሎቶች
    • አርቲክሎች
    • ዜናዎች
    • ጋለሪ
  • ክፍት የስራ ማስታወቂያ
ዓርብ ፣ ግንቦት 30 ቀን 2025
/ Categories: CASSATION, Cassation

የአቶ ከበደ ተክለማርያም ወራሾች፡-እነ አቶ ደረጀ ከበደ.(4ሰዎች)እና እነ አቶ ደረጀ ተስፋዬየሰ/መ/ቁ253101

ጉዳዩ የውርስ ማጣራትን ተከትሎ የቀረበ የሚስት የንብረት ድርሻን የሚመለከት ነው፡፡ክርክሩ የተጀመረው በፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ሲሆን የአመልካቾች አዉራሽ ሟች አቶ ከበደ ተክለማሪያም አመልካች፣የአሁኑ ተጠሪዎች በሌላ በኩል ተጠሪዎች በመሆን ተከራክረዋል፡፡ የአመልካቾች አውራሽ በስር ፌደራል መጀመሪያ ደረጃ  ፍርድ ቤት ያቀረቡት አቤቱታ ይዘት በአጭሩ ልጃቸው ሟች ወ/ሮ ጥሩዓለም ከበደ ልጅ ሳይወልዱ በመሞታቸው ከባለቤታቸው አስር አለቃ ተስፋዬ ደስታ ጋር ያፈሩት በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 12 የቤት ቁጥር 682 የሆነው ንብረት እና ከቤቱ የተሰበሰበው የኪራይ ሀብት በውርስ አጣሪ ተጣርቶ የድርሻዬ እንዲለይ በሚል ያቀረቡ ሲሆን የሟቿ አባት የሆኑት አቶ ከበደ ተክለማሪያም በመሞታቸው አመልካቾች በተተኪ ወራሽነት ወደ ክርክሩ እንዲገቡ ተደርጓል፡፡ተጠሪዎችም በቀረበው አቤቱታ ላይ መልስ በመስጠት የአቤቱታው መነሻ የሆነው የውርስ ሀብቱም ተጣርቶ እንዲቀርብ ተደርጓል፡፡በውርስ አጣሪው ተጣርቶ የቀረበው ርፖርት ይዘትም የአስር አለቃ ተስፋዬ ደስታ በመ/ቁ 158482 ህዳር 03 ቀን 2013 ዓ.ም የውርስ ሀብት ተጣርቶ በጸደቀው የውርስ ሀብት ሪፖርት አስር አለቃ ተስፋዬ ደስታ ሰኔ 09 ቀን 1995 ዓ.ም ባደረጉት ኑዛዜ መሰረት የክርክር መነሻ በሆነው ቤት እና ይዞታ ላይ የሟች ወ/ሮ ጥሩዓለም ከበደ ድርሻ 1/4ኛ ነው የሚል ውሳኔ የተሰጠ በመሆኑ አመልካቾች የሟቿን ድርሻ የቤቱን እንደዚሁም ከኪራይ የሚገኘውን ገቢ 1/4ኛ ድርሻ እንዲካፈሉ የሚል ነው፡፡ግራ ቀኙም በቀረበው የውርስ አጣሪ ሪፖርት ላይ ያላቸውን አስተያየት የሰጡ ሲሆን ፍ/ቤቱም የሟች አስር አለቃ ተስፋዬ ደስታ የውርስ ሀብት በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት በመ/ቁ 158482 ላይ ተጣርቶ የፀደቀ ሲሆን በዚህ የጸደቀው የውርስ አጣሪ ሪፖርት ላይ የውርስ ሀብት የሆነውን ቤት ሟች አስር አለቃ ተስፋዬ ደስታ በሰኔ 09 ቀን 1995 ዓ.ም ባደረጉት ኑዛዜ  በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 12 የቤት ቁጥር 682 ከሆነው ቤት እና ይዞታ ላይ የሟች ወ/ሮ ጥሩዓለም ከበደ ድርሻ 1/4ኛ መሆኑን ፍ/ቤቱ የቀረበው በውርስ አጣሪ ሪፖርት ተረጋግጧል፣አመልካቾችም ይህን ውሳኔ አላሻሩም፣ከቤት ቁጥር 682 ላይ የሟች ወ/ሮ ጥሩዓለም ከበደ የሚስትነት ድርሻ ግማሽ ድርሻ እንደሆነ የሚገልጽ ውሳኔ አላቀረቡም፣አመልካቾች ይህ ውሳኔ ስለመሻሩም ያቀረቡት ማስረጃ የለም፣ ወ/ሮ ጥሩዓለም ከበደ የሟች አስር አለቃ ተስፋዬ ደስታ ሚስት ስለመሆኗ እና ቤት እና ይዞታውን በጋራ አፍርተዋል በሚል የተሰጠ ውሳኔ አልቀረበም፣ ሟች ወ/ሮ ጥሩዓለም ከበደ ከሟች አስር አለቃ ተስፋዬ ደስታ ጋር በመሆን ያፈሩ በመሆኑ ግማሹ የሟች ወ/ሮ ጥሩዓለም ከበደ የሚስትነት ድርሻ ሊሆን ይገባል የሚል ክርክር ሊቀርብ የሚገባው በቤተሰብ ችሎት እንጂ በዚህ በተያዘው ችሎት ባለመሆኑ የሟች ወ/ሮ ጥሩዓለም ከበደ ድርሻ ከሆነው                                                                                                                                                                      1/4ኛ ድርሻ ላይ አመልካቾች እያንዳንዳቸው 1/4ኛ ድርሻ አላቸው።የቤት ኪራይን ገቢን በተመለከተ የተሰበሰበው ገቢ በአጠቃላይ ብር 444,400 ስለሆነ ከዚህ ገንዘብ ላይ ሟች ወ/ሮ ጥሩዓለም ከበደ ድርሻ ብር 111,100 በመሆኑ ሟች ወ/ሮ ጥሩዓለም ከበደ ድርሻ ላይ አመልካቾች እያንዳንዳቸው 1/4ኛ ማለትም ብር 27,775 ብር የሚደርሳቸው ሆኖ ለተለያዩ ጉዳዮች የወጣው ወጪ ብር 108,259.11 በመሆኑ የሟች ወ/ሮ ጥሩዓለም ከበደ ድርሻ ብር 27,064.78 ስለሆነ ከዚህ ላይ አመልካቾች እያንዳንዳቸው ብር 6943.75 የሚለከፍሉት ውርስ ሃብት ዕዳ ይሆናል በማለት በውርስ አጣሪ የቀረበውን ሪፖርት አጽድቆታል፡፡መልካም ንባብ…

Print
2280

Documents to download

  • 253101(.pdf, 1.08 MB) - 281 download(s)

Categories

  • 2011 Expand/Collapse
  • 2012 Expand/Collapse
  • 2013 Expand/Collapse
    መገናኛ
  • ስልክ : +251-11-1-55-34-00 /
  •          +251-11-1-11-04-32
  • ፋክስ : +251 111-550278 /
  •          +251 111-565583
  • ኢሜል : fscpublicrelation@gmail.com
  • አድራሻ ፡ 6 ኪሎ አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
ፈጣን አገናኝ
  • ስለፍርድ ቤቱ 
  • ኢ-ፋይሊንግ
  • የቀን መቁጠሪያ
  • ዜና መግለጫዎች
  • የጉዳዮች መከታተያ
  • በተደጋጋሚ የሚቀርቡ ጥያቄዎች
    ያግኙን
  • Privacy Policy
  • |
  • Site Map
Copyright 2026 by Federal Supreme Court
Powered By Bsquare IT Solutions