የአቶ ዳምጤ አድማሱ እና ወ/ሮ ሀረገወይን ብርሃነመስቀል ሰበር መዝገብ ቁጥር - 250606
ጉዳዩ የተጀመረው በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ነው፡፡ አመልካች 2ኛ ተከሳሽ ተጠሪ ከሳሽ ሲሆኑ አሁን የክርክሩ አካል ያልሆነው አቶ ሽመልስ መንገሻ 1ኛተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ የስር ከሳሽ የአሁን ተጠሪ በስር ተከሳሾች ላይ ያቀረቡት ክስ ይዘት ከሳሽ ባልሰጠሁት ውክልና ውክልና እንደሰጠሁት በማድረግ በሀሰተኛ ውክልና ከ 2ኛ ተከሳሽ ጋር የቤት ሽያጭ ውል ፈፅመዋል፡፡ የተሸጠው ቤት የከሳሽና 1ኛ ተከሳሽ የጋራ ንብረት ነው፡፡ የከሳሽና 1ኛ ተከሳሽ ጋብቻ በፍርድ ቤት ፈርሷል፡፡ የተሸጠው ቤት የከሳሽና 1ኛ ተከሳሽ የጋራ ቤት በመሆኑ ያለ እኔ ስምምነት የተፈፀመ የሽያጭ ውል በተሻሻለው የቤተሰብ ህግ አንቀፅ 68 መሰረት የቤት ሽያጭ ውል እንዲፈርስ የሚል ነው፡፡የስር 1ኛ ተከሳሽ መጥሪያ በቤቱ ላይ ቢለጠፍም መልስ ባለማቅረቡ መብቱ ታልፏል፡፡ ከ 2ኛ ተከሳሽ የአሁኑ አመልካች የተሰጠው በአጭሩ የቤት ሽያጭ ውል በህጋዊ መንገድ በሰነዶች ምዝገባና ማረጋገጫ ፅ/ቤት ቀርቦ ተመዝግቧል፡፡ ቤቱን የገዛሁት ከከሳሽና ከ 1ኛ ተከሳሽ ወኪል ላይ ገዝቻለሁ የከሳሽና 1ኛ ተከሳሽ ወኪል የሆኑት ወ/ሮ ታሪኳ ገዛኸኝ በውል አዋዋይ ፊት የገዛሁት ስለሆነ ውሉ ሊፈርስ አይገባም 2ኛ ተከሳሽ የቅን ልቦና ገዥ ስለሆንኩ ውሉ ሊፈርስ አይገባም፡፡ ቤቱን ከተረከብኩ በኃላ በቤቱ ላይ ብር 600,000 በላይ አውጥቼ ግንባታ ፈፅሚያለሁ ለቤት ግዥ ካወጣሁት ከብር 3,200,000 ጋር በአጠቃላይ 3,800,000 ብር ወጪ አውጥቻለሁ ውሉ ሊሰረዝ አይገባም ተብሎ እንዲወሰን በማለት ተከራክሯል፡፡መልካም ንባብ…
1842
Documents to download
-
250606(.pdf, 835.71 KB) - 225 download(s)