የካፕቴን ሲዶኔ ኬቭን ሁበርት ጆርጅስ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰ.መ.ቁ 257998
የጉዳዩ አመጣጥ አመልካች በስር የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድቤት በተጠሪ ላይ ባቀረቡት ክስ ተጠሪ አመልካችን በኢሲ ኤክስፓት ፓይለት በውጭ ዜጋ አብራሪነት በ22/1/2011ዓ.ም በተፈረመ የስራ ቅጥር ውል ለተወሰነ ግዜ የቀጠረ ሲሆን በ26/2/2011ዓ.ም በተጻፈ ግዜያዊ የቅጥር ደብዳቤ ደግሞ የአመልካች ወርሃዊ ደመወዝ የአሜሪካን ዶላር 9000(ዘጠኝ ሺህ) እንደሚሆን አረጋግጦለታል፡፡ ከኮቪድ ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ ተጠሪ አመልካችን ከየካቲት 20 ቀን 2012ዓ.ም ጀምሮ ክፍያ በሌለው እረፍት ላይ እንዲቆይ የወሰነ ሲሆን ወረርሽኙ ጋብ ካለ በኋላ በህዳር ወር 2014ዓ.ም ስራውን የሚቀጥልበትን ሁኔታ ለመነጋገር አመልካች አዲስአበባ በመጣበት ወቅት ከበረራ ስራ ክፍል የሰው ሀይል ሃላፊ ከሆኑት ከአቶ ምህረቱ ቦርሳሞ የተነገረው ክፍያ በሌለው እረፍት ላይ እንዲቆይ ከተወሰነበት ግዜ ጀምሮ ከአመልካች ጋር ያለው የስራ ግንኙነት የተቋረጠ መሆኑን በመሆኑ አመልካች በስራው የማይቀጥል ከሆነ ለስልጠና ሲባል ተጠሪ የያዘበትንና ተመላሽ ሊያደርግለት የሚገባውን ዩኤስዲ 15‚000 ተመላሽ እንዲደረግለት ጠይቋል፡፡መልካም ንባብ…
2339
Documents to download
-
257998(.pdf, 877.79 KB) - 310 download(s)