ለቀድሞዎቹ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንት እና ም/ፕሬዚደንት ለክብርት ወ/ሮ መአዛ አሸናፊና ለክቡር አቶ ሰለሞን አረዳ የካቲት 11 ቀን 2015 ዓ.ም በካፒታል ሆቴል አሸኛኘት ተደረገላቸው፡፡
አሸኛኘቱን ያደረጉት አዲስ የተሾሙት የፍ/ቤቱ ፕሬዚደንት እና ም/ፕሬዚደንትነት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምሕረት እና ክብርት ወ/ሮ አበባ እምቢአለን ጨምሮ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞችና የሶስቱም የፌደራል ፍ/ቤቶች አመራሮች ናቸው፡፡