የሰበር ውሳኔዎች

 

ሰባት ዳኞች በተሰየሙበት የሰበር ችሎት...

በሐይማኖት ተቋማት ውስጥ አስተዳደራዊ ተግባርን ለማከናወን በተሰማሩ ሰራተኞች የሚነሱ  የስራ ክርክሮችን በተመለከተ ፍርድ ቤቶች የስራ ክርክሩን ተቀብለው አከራክረው ለመወሰን ህጋዊ የዳኝነት ስልጣን ያላቸው ስለመሆኑ ትርጉም... Read more

ሰባት (7) ዳኞች በተሰየሙበት ችሎት...

ከ2002 ዓ.ም እስከ 2017 ዓ.ም በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰባት (7) ዳኞች በተሰየሙበት ችሎት የተሰጡ አስገዳጅ የሰበር ውሳኔዎችን ያጠቃለለ መጽሐፍ በልዮ ዕትም ለንባብ ምቹ ሆኖ ቀርቧል። Read more

ወ/ሮ የማርውሃ ወርቅነህ እና እነ ወ/ሮ...

የጉዳዩ አመጣጥ ባጭሩ ሲታይ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ተጠሪዎች ከሳሽ አመልካች ደግሞ ጣልቃ ገብ ሆነው ተከራክረዋል፡፡ ተጠሪዎች በቀን 11/09/2013 ዓ.ም ጽፈው ባቀረቡት አቤቱታ የእናታቸው ወ/ሮ ሸዋነሽ ስመኝ... Read more

ጨመሬ ቶሎሳ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ...

የአሁን አመልካች በምዕራብ ወለጋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በ/መ/ቁ 47863 እና በመ/ቁ በመ/ቁ 47862 በሁለቱም መዝገቦች ላይ 2ኛ ተከሳሽ ሲሆን ተጠሪ በአመልካች ላይ ያቀረበው የክስ ይዘትም አመልካች የኢትዮጵያ የፌዴራል ቡና... Read more
12345678910Last
«February 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
2627282930311
2345678
9101112131415
16171819202122
2324252627281
2345678

ፍርድ ቤቱ የዲጂታል የሀብት ማስመዝገብ መርሐ-ግብር አስጀመረ

2102

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የዲጂታል የሀብት ምዝገባና ማሳወቅ መርሐ-ግብር በፌደራል ፍርድ ቤቶች መጀመሩን መጋቢት 8 ቀን 2014 ዓ/ም በፍርድ ቤቱ የስብሰባ አዳራሽ በተካሔደ ሥነሥርዓት ይፋ አደረጉ፡፡

በፌደራል ፍርድ ቤቶች የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ተግባራዊ የሚደረገውን የዲጂታል የሀብት ምዝገባና ማሳወቅ መርሐ-ግብር የተጀመረው ፍርድ ቤቱ እና የፌደራል የሥነምግባር እና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን በጋራ ባዘጋጁት ሥነሥርዓት ላይ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንት ክብርት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ ሀብታቸውን እንዲያስመዘግቡ በተከናወነ ሥነሥርዓት ነው፡፡

የፍ/ቤቱ ዳኞች በጉዳዮች ፍሰት አስተዳደር እና በመዛግብት...

ፍርድ ቤቱ 20 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ከመንግስት ማግኘቱም ተጠቁሟል

3042

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞች በ2014 የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የፍትሐብሔር ጉዳዮች ፍሰት አስተዳደርን ተግባራዊ በማድረግ እና በመዛግብት አፈጻጸም ያስመዘገቡት ውጤት አበረታች በመሆኑ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባው የፍርድ ቤቱ ፕሬዚደንት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ ገለጹ፡፡

ክብርት ፕሬዚደንትዋ ይህን የገለጹት የፍርድ ቤቱ ከፍተኛ አመራሮች፣ ዳኞች እና ረዳት ዳኞች በተሳተፉበትና በፌደራል ፍ/ቤቶች የአምስት ዓመታት (2014-2018 ዓ.ም) ስትራቴጂያዊ ዕቅድ ዋና ዋና ይዘት እና በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የችሎቶችና ዳኞች የ2014 የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የመዛግብት አፈጻጸም ላይ መጋቢት 3 ቀን 2014 ዓ.ም በካፒታል ሆቴል የተደረገውን ውይይት ሲያጠቃልሉ ባደረጉት ንግግር ነው፡፡

የፌደራል ፍርድ ቤቶች ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን በፓናል...

1891

በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ111ኛ ጊዜ፣ በአገራችን ደግሞ ለ46ኛ ጊዜ እየተከበረ የሚገኘውን ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን (ማርች 8) የፌደራል ፍርድ ቤቶች የካቲት 29 ቀን 2014 ዓ.ም በካፒታል ሆቴል በፓናል ውይይት አከበሩ፡፡

የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት የፓናል ውይይቱን በንግግር ሲከፍቱ ባደረጉት ንግግር የሴቶች የሲቪልም ሆነ የፖለቲካ መብት እና ተሳትፎ ከኢኮኖሚ መብት ጋር ተያያዥ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ለዚህም ማሳያው የግል ገቢ የሌላት ሴት ከሚበድላት ባል ጋር ለመኖር እንደምትገደድና አማራጭ የሥራ ዕድል የሌላት ሴትም የመጥፎ አለቃን እብሪትና ትንኮሳ ችላ ለመኖር የምትገደድ መሆንዋ ትስስሩን እንደሚያሳይ አስረድተዋል፡፡

ክብርት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ አገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ...

1672

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክብርት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሹመታቸውን ያጸደቀላቸው የኢትዮጵያ አገራዊ የምክክር ኮሚሽን አመራሮች የቃለመሀላ ሥነ-ሥርዓት ዛሬ የካቲት 14 ቀን 2014 ዓ.ም አስፈጽመዋል፡፡

ክብርት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ የአገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ስራ ውጤታማ የሚሆነው ከባለድርሻ አካላት እና ከሕብረተሰቡ አስፈላጊው ትብብርና ድጋፍ ሲሰጠው መሆኑን በቲውተር ገጻቸው ገልጸዋል፡፡

ክብርት ፕሬዝደንቷ ከምክክር ኮሚሽኑ ብዙ ይጠበቃልም ብለዋል::

First6364656668707172Last